Fana: At a Speed of Life!

ከእሥራኤል ጋር ትብብራችን በተለያዩ መስኮች ተጠናክሮ ቀጥሏል – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከእሥራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር ጋር ተወያዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ጉብኝት በማድረግ ላይ ካሉት የእሥራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ሳር ጋር በኢትዮ-እሥራኤል ግንኙነት ላይ ፍሬያማ ውይይት አካሂደናል ብለዋል።

ሁለቱ ሀገሮቻችን በታሪክ ሥረ መሠረት ላይ የተገነባ ረዥም ዘመን የቆየ ግንኙነታቸውን ዛሬም ቀጥለዋል በማለት ገልጸው፤ ዛሬ ትብብራችን በኢኮኖሚያዊ፣ በፖለቲካዊ፣ በዲፕሎማሲያዊ፣ በማኅበራዊ እና በሌሎችም መስኮች ላይ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.