Fana: At a Speed of Life!

ከ23 ሚሊየን በላይ ዜጎች በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ይሳተፋሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በዘንድሮው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ23 ሚሊየን በላይ ዜጎች ይሳተፋሉ አለ፡፡

የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቱ 14 መርሐ ግብሮች እንዳሉት በሚኒስቴሩ የወጣቶች ብሔራዊ እና የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስፋፊያ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዐቢይ ኃ/መለኮት ተናግረዋል።

የዳበረ የመደጋገፍ ዕሴትን ለማሳደግ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የላቀ ሚና እንዳለው አስረድተዋል፡፡

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተሳትፎን በማሳደግ አሠራሩን መዋቅራዊ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

በስንታየሁ አበበ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.