Fana: At a Speed of Life!

በጋምቤላ ክልል 12 ሺህ 662 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጋምቤላ ክልል 12 ሺህ 662 ተማሪዎች በወረቀት እና በኦንላይን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ የሚያስችላቸውን ዝግጅት አድርገዋል አለ የክልሉ ትምህርት ቢሮ፡፡

በዚሁ መሠረት በጋምቤላ እና ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናው በተያዘለት መርሐ ግብር በወረቀት እንደሚሰጥ የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ፖክ ካዊች ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ 990 የማኅበራዊ እና ተፈጥሮ ሣይንስ ተማሪዎች በኦንላይን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ እንደሚወስዱ አስረድተዋል፡፡

በወረቀት እና በኦንላይን ለሚሰጡት ፈተናዎችም ለተማሪዎች የልምምድና የሞዴል ፈተናዎች መሰጠታቸውን ነው የገለጹት፡፡

በዮሐንስ ደርበው

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.