Fana: At a Speed of Life!

የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ቀጣይነት ባለው መልኩ ማጠናከር ይገባል – አቶ አሻድሊ ሀሰን

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ቀጣይነት ባለው መልኩ በመተግበር ይበልጥ ማጠናከር ይገባል አሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን።

“በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ሐሳብ የ2017 የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መደረክ ዛሬ በአሶሳ ከተማ ተካሄዷል።

በመድረኩ ላይ አቶ አሻድሊ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ካለው ጠቀሜታ አኳያ ቀጣይነት ባለው መልኩ ተጠናክሮ ሊተገበር እንደሚገባ ገልጸው÷ ወጣቶች ሕብረተሰቡን በማገልገል ለሀገር ያላቸውን ፍቅር የሚገልፁበት መልካም አጋጣሚ ነው ብለዋል።

በአረንጓዴ አሻራ፣ አካባቢ ጥበቃ፣ ደም ልገሳ እና ቤት እድሳት የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች የሕብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ መልካም ተግባራት መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተጨማሪም ወጣቶች በክልሉ ዘላቂ ሠላም እንዲሰፍን በሚደረገው ጥረት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

ወጣቶች የክረምት ወራትን ሕብረተሰቡን በማገዝ ተሳትፏቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ርዕሰ መስተዳድሩ÷ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ይበልጥ እንዲለመድ እና የወጣቶች ተሳትፎ እንዲያድግ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የክልሉ ሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ አለምነሽ ይባስ በበኩላቸው÷ በዘንድሮው የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከ100 ሺህ በላይ ወጣቶችን ተሳታፊ ለማድረግ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል።

ከዚህ በፊት በተከናወኑ የበጎ በፈቃድ አገልግሎቶች በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ያደረጉ የቤት እድሳት፣ ደም ልገሳ እና ሌሎች ተግባራት እንደተከናወኑ ማንሳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

በክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ መድረክ ላይ የክልል፣ የዞን እና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮችና ወጣቶች ተገኝተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.