Fana: At a Speed of Life!

በቀጣዩ ዓመት በቴክኒክ ሙያ ዘርፍ የዶክትሬት ዲግሪ ትምህርት ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቅቋል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በቴክኒክ ሙያ ዘርፍ የዶክትሬት ዲግሪ (ሌቪል 8) ትምህርት ስልጠና ለመስጠት ዝግጅት ተጠናቅቋል አሉ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል።

የኢፌዴሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺህ ተማሪዎችን አስመርቋል፡፡

ወ/ሮ ሙፈሪሃት በዚህ ወቅት እንዳሉት÷የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ወሳኝ ነው ።

መንግስት ዘርፉን በማጠናከር ዓለም የደረሰበት ደረጃ ለማድረስ ባለፉት ዓመታት በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን አንስተዋል።

ይህንን ተከትሎ ዘርፉ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ማግኘቱን ጠቅሰው ÷ በ2017 የዓለም አቀፍ የክህሎት ህብረተሰብ አባል መሆን የተቻለበት ውጤታማ ዓመት መሆኑን ተናግረዋል።

ዘርፉ የሀገርን ብልጽግና ለማረጋገጥ ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይም የተገኘውን ውጤት ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።

በቀጣይ ዓመት በሌቭል 8 ዶክትሬት ዲግሪ ትምህርት ለመጀመር ዝግጅት የተጠናቀቀ ሲሆን÷ ይህም ዘርፉን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ያስችላል ብለዋል።

የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች በሰለጡኑበት ዘርፍ ሀገራቸውን እና ሕዝባቸውን በታታሪነት እንዲያገለግሉ ሚኒስትሯ ጥሪ ማቅረባቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.