Fana: At a Speed of Life!

በአማራ ክልል የቱሪዝም ልማቱን በማነቃቃት ኢኮኖሚያዊ አበርክቶውን ለማጉላት እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአማራ ክልል የቱሪዝም ዘርፉን በማነቃቃት ለአገራዊ ኢኮኖሚያዊ እድገትና ለህዝብ ተጠቃሚነት የሚኖረውን አበርክቶ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ።

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር በቱሪዝም እንቅስቃሴ፣ በቅርስ ጥበቃና ፓርኮች ልማት ዙሪያ የምክክር መድረክ ዛሬ በባህር ዳር አካሄዷል።

አቶ አረጋ ከበደ በመድረኩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት እንዳሉት÷ በክልሉ በተለያዩ ችግሮች የተጎዳውን የቱሪዝም ዘርፍ ለማነቃቃት ከሚኒስቴሩ ጋር በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል።

የክልሉ ሰላም እየተሻሻለ በመምጣቱ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና የለሙትን በማስተዋወቅ ከዘርፉ ማግኘት የሚገባውን ጥቅም ለማግኘት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ የሚገኙ እንደ አንኮበር፣ ይስማ ንጉስ፣ ውጫሌና ሌሎች የመዳረሻ ቦታዎችን በማልማት የቱሪዝም ልማቱን ለማሳደግና የቱሪስት የቆይታ ጊዜን ለማራዘም እየተሰራ ነው ብለዋል።

የቱሪዝም ሃብቱን ለማሳደግ መሰረተ ልማትን ለማስፋፋትና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ለማሻሻል ሁሉን አቀፍ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝም አመልክተዋል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በበኩላቸው÷ ሚኒስቴሩ በክልሉ ያሉ ዕምቅ የቱሪዝም ሃብቶችን በማልማትና በማስተዋወቅ ረገድ የውጭና የሀገር ውስጥ ቱሪስቶችን ለመሳብ በጋራ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማልማትና ነባር ቅርሶችን በመጠገን የክልሉን ህዝብ ከቱሪዝም ዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝም አብራርተዋል።

ክልሉ ሰላምን ከማረጋገጥ ጎን ለጎን በርካታ የልማት ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን ተገንዝበናል ያሉት ሚኒስትሯ÷ ቱሪዝም ሰላምን አጥብቆ የሚሻ መሆኑን በመገንዘብ መስራት ይገባል ማለታቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.