Fana: At a Speed of Life!

በብሔራዊ ሙዚየም የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶች የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ ያሳያሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም የሚገኙ ታሪካዊ ቅርሶች የኢትዮጵያን ገናና ታሪክ የሚያሳዩ ናቸው አሉ ሙዚየሙን የጎበኙ የጤና ሙያተኞች።

“ኢኖቬሽን ለሁለንተናዊ የጤና ሽፋን” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ በተካሄደው ዓለም አቀፍ የጤና ኢኖቬሽንና ጥራት ጉባኤ የተሳተፉ ሙያተኞች ብሔራዊ ሙዚየምን ዛሬ ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም ሙዚየሙ የኢትዮጵያን ታሪክና ቅርስ በአንድ ላይ ሰንዶ እንደያዘ መመልከታቸውን መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

በሙዚየሙ የሚጎበኙ ቅርሶችና ታሪካዊ ጽሁፎች ኢትዮጵያን ለማስተዋወቅ ጉልህ ፋይዳ እንዳላቸው ተገንዝቢያለሁ ያሉት ዶክተር ነጋሽ ስዩም፤ ታሪካዊ ቅርሶች ተደራጅተው መገኘታቸው የኢትዮጵያን ገናና ታሪክና ቀደምትነት ለማሳየት ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል ብለዋል።

ሌላኛው አስተያየት ሰጪ አሚር አብደላ በበኩላቸው፤ ጉብኝቱ የኢትዮጵያን ታሪክና ቅርስ ለማወቅ እድል የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው፤ ሙዚየሙን ማደስ ጨምሮ የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ኢትዮጵያ በፈጣን እድገት ላይ መሆኗን በተግባር የሚያሳዩ ስለመሆናቸውም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የባለ ብዙ ታሪክ፣ ባህልና የቱሪስት መዳረሻ መሆኗን ለሌሎች ለማሳወቅ በሙዚየሙ የተቀመጡ ታሪካዊ መዛግብትና ቅርሶች ጥሩ ማሳያ እንደሚሆኑ የገለጹት ደግሞ አቶ አበባው ደርሶ ናቸው።

 

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

 

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.