በሐረማያና ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከላት እየገቡ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሐረማያ እና ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ወደ ፈተና ማዕከላት መግባት ጀምረዋል፡፡
ተፈታኝ ተማሪዎቹ ወደ ማዕከላቱ ሲገቡ የዩኒቨርስቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ 7 ሺህ 29 ተማሪዎች በወረቀት የሚፈተኑ ሲሆን፤ 592 ተማሪዎች ደግሞ በበይነ መረብ ፈተናውን እንደሚወስዱ የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኡርጌ (ፕ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ገልፀዋል።
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ 1 ሺህ 72 ተማሪዎችም ወደ ዩኒቨርሲቲው እየገቡ መሆናቸውን የዩኒቨርሲቲው ሬጂስትራር ጉዳዮች ዳይሬክተር ጂብሪል አልብዱልቃድር (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን አብራርተዋል፡፡
በወረቀትና በበይነ መረብ የሚፈተኑት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተናቸውን ከኩረጃ በፀዳ መልኩ ማከናወን እንዲችሉ ከወዲሁ አስፈላጊው ጥንቃቄ እየተደረገ እንደሆነ አመላክተዋል።
የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡
በተሾመ ኃይሉ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!