Fana: At a Speed of Life!

በጥገና ምክንያት ዛሬ ሌሊት በተወሰኑ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ይቋረጣል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ ሴንተር ወይም በሜክሲኮ ማከፋፈያ ትራንስፎርመር ላይ በሚከናወን አስቸኳይ የጥገና ሥራ ምክንያት ዛሬ ሌሊት በተወሰኑ አካባቢዎች ኃይል ይቋረጣል አለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፡፡

የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለፁት፤ ዛሬ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ጀምሮ በሚከናወነው የጥገና ሥራ ምክንያት ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች ኃይል ይቋረጥባቸዋል።

የማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ልዩ ጥገና እንደሚደረግ ገልጸው፤ ከጥገናዎቹ መካከል አንደኛው ዛሬ ሌሊት የሚደረገው ጥገና አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።

አስቸኳይ ጥገና የሚደረገው ትራንስፎርመሮች ጭነት እንዳይበዛባቸው ታሳቢ ተደርጎ እንደሆነ ጠቅሰው፤ ጥገናው የአገልግሎት አሰጣጡን የተሻለ ለማድረግ በማሰብ ነው ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት የኃይል አጠቃቀም እያደገ በመምጣቱ የትራንስፎርመሮችን ደህንነት የማረጋገጥ ሥራ አስቀድሞ መሰራት እንዳለበት አንስተዋል።

በመሆኑም በዛሬው ሌሊት ልዩ ጥገና ከሚካሄድባቸው መስመሮች ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች ኃይል እንደሚቋረጥባቸው ጠቁመዋል።

በመሆኑም ሜክሲኮ፣ ቄራ፣ ገነት ሆቴል፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አካባቢ፣ መስቀል ፍላወር፣ ወሎ ሰፈር፣ መስቀል አደባባይ፣ ባምቢስ እና አካባቢው እንደሚገኙበት አስረድተዋል፡፡

የጥገና ሥራው እስከሚጠናቀቅ ድረስም በተጠቀሱት አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መልዕክት መተላለፉን ገልጸዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.