Fana: At a Speed of Life!

የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና እየተሰጠ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በሁሉም የመፈተኛ ማዕከላት መሰጠት ጀምሯል አለ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፡፡

የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ÷ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት በኦንላይንና በወረቅት እየተሰጠ እንደሚገኝ ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና በተፈጥሮ ሳይንስና በማህበራዊ ሳይንስ በአጠቃላይ 608 ሺህ 588 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ አንስተዋል፡፡

በአራት ዙር በሚሰጠው ፈተና 140 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን እንሚወሰዱ ነው የገለጹት፡፡

ተማሪዎች ለፈተና የተከለከሉ ነገሮችን መያዝ እንደሌለባቸው ያሳሰቡት (ዶ/ር) እሸቱ ÷ ፈተናውን ተረጋግተው መፈተን እንዳለባቸውም መክረዋል፡፡

ባለፉት ቀናት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ መፈተኛ ማዕከላት ሲገቡ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡

የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23 ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.