Fana: At a Speed of Life!

ሞናኮ አንሱ ፋቲን በውሰት አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፈረንሳዩ ክለብ ሞናኮ ስፔናዊውን የፊት መስመር ተጫዋች አንሱ ፋቲን በውሰት ውል አስፈርሟል፡፡

ሞናኮ ስፔናዊውን የፊት መስመር ተጫዋች በ11 ሚሊየን ዩሮ የመግዛት አማራጭ ባካተተ የውሰት ውል ወደ ስብስቡ ቀላቅሏል፡፡

በ2024/25 የውድድር ዓመት አንሱ ፋቲ ለባርሴሎና በሁሉም ውድድር 10 ጨዋታዎች ላይ ተሳትፏል፡፡

የ22 ዓመቱ ስፔናዊ የፊት መስመር ተጫዋች አንሱ ፋቲ በባርሴሎና ቤት እስከ 2028 የሚያቆይ ኮንትራት እንዳለው ይታወቃል፡፡

አንሱ ፋቲ በውሰት ውሉ መሰረት በሞናኮ እስከ ሰኔ 2026 ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡

ከካታላኑ ክለብ ባርሴሎና በውሰት ውል ሞናኮን የተቀላቀለው አንሱ ፋቲ በሞናኮ ቤት 31 ቁጥር ማልያን እንደሚለብስም ተረጋግጧል፡፡

የፈረንሳዩ ክለብ ሞናኮ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ፖል ፖግባ፣ ኤሪክ ዳየር እና አንሱ ፋቲን በማስፈረም ቡድኑን የማጠናከር ስራ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.