Fana: At a Speed of Life!

37 ቶን የወርቅ ምርት ለውጭ ገበያ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2017 በጀት ዓመት 37 ቶን የወርቅ ምርት ለውጭ ገበያ ቀርቧል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው፡፡

በማብራሪያቸውም ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን አቅም ያላት ሀገር መሆኗን አውስተው÷ ይሁን እንጂ በቀደሙ መንግስታት ለዘርፉ ትኩረት ሳይሰጠው መቆየቱን ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ በዘርፉ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው÷ በ2017 በጀት ዓመት 37 ቶን የወርቅ ምርት ለውጭ ገበያ መቅረቡን አስረድተዋል፡፡

ባለፈው በጀት ዓመት አራት ቶን ወርቅ ብቻ ወደ ውጪ ተልኮ እንደነበር ጠቁመው÷ በዘንድሮው ዓመት በዘርፉ ከፍተኛ እመርታ መመዝገቡን አብራርተዋል፡፡

በዘርፉ ለውጭ ገበያ ከቀረበ ምርትም 3 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ ተገኝቷል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፡፡

በመላኩ ገድፍ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.