Fana: At a Speed of Life!

“ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶችን ከሩቅ የማስቀረት ብቃት ያለው ሠራዊት ተገንብቷል” ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሊከሰቱ የሚችሉ ስጋቶችን ከሩቅ የማስቀረትና ብሄራዊ አደጋ ቢከሰት በብቃት መቀልበስ የሚችል ሠራዊት ተገንብቷል አሉ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፡፡

የመከላከያ አዛዥነትና ስታፍ ኮሌጅ ለ15ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን ከሁሉም የጦር ክፍሎች የተወጣጡ ከፍተኛ መኮንኖች በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ የሰራዊቱ አመራሮች፣ አምባሳደሮችና ወታደራዊ አታሼዎች ተገኝተዋል።

የመከላከያ አዛዥነት ስታፍ ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀኔራል ሙሉጌታ አምባቸው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ ተመራቂ ከፍተኛ መኮንኖች በቀጣይ የሚሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃት ለመፈጸም የሚያስችል ስልጠና ወስደዋል።

የወታደራዊ አመራር ሥልጠናው ዘመኑ የሚጠይቀውን ዕውቀት በመጨበጥ ኢትዮጵያን በላቀ ደረጃ ማገልገል እንዲችሉ የሚያዘጋጃቸው መሆኑንም ነው የተናገሩት።

ኮሌጁ ከኢትዮጵያ በተጨመሪ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ወታደራዊ አመራሮችን እያፈራ ያለ ተቋም መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በየሻምበል ምህረት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.