ካይል ዎከር ለበርንሌይ ፈረመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የማንቼስተር ሲቲ የክንፍ ተከላካይ ካይል ዎከር በርንሌይን በ5 ሚሊየን ፓውንድ ተቀላቅሏል፡፡
የ35 ዓመቱ ዎከር ባለፈው የውድድር ዓመት ለማንቼስተር ሲቲ 15 ጊዜ የተሰለፈ ሲሆን÷ በጥር የዝውውር መስኮት ወደ ጣልያኑ ኤሲሚላን በመሄድ መጫወቱ ይታወሳል፡፡
በኢቲሃድ ቆይታው 17 ዋንጫዎችን ያሳካው ዎከር ÷ በ2023 የውድድር ዓመት ሲቲ ባለ የሶስትዮሽ ዋንጫ ባለቤት ሲሆንም የቡድኑ አባል ነበር፡፡
በፈረንጆቹ 2017 ለዜጎቹ ከቶትንሃም ሆትስፐር የፈረመው ካይል ዎከር 319 ጨዋታዎች ላይ መሰለፉ ተመላክቷል፡፡
በ2024 ከሊጉ ወደ ሻምፒየንሺፑ የወረደው በርንሌይ ባለፈው የውድድር ዓመት ዳግም ወደ ሊጉ ማደጉ ይታወቃል፡፡
በርንሌይ ቀደም ሲል አክሴል ቷንዜቤ፣ ሃርትማን፣ ማክስ ዌስ እና ሉም ቻውናን የመሳሳሉ ተጫዋቾችን እንዳስፈረመ ስካይ ስፖርት ዘግቧል፡፡
በተመሳሳይ ማንቼስተር ዩናይትድ የ18 ዓመቱን የመሃል ተከላካይ ዲዬጎ ሊዮንን ከፓራጓዩ ክለብ ሴሮ ፖርቴኖ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
በአቤል ንዋይ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!