ባየርን ሙኒክ ከዓለም ክለቦች ዋንጫ ተሰናበተ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ክለቦች ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ የፈረንሳዩ ፒ ኤስ ጂ የጀርመኑን ባየርን ሙኒክ 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅሏል፡፡
የፒ ኤስ ጂን የማሸነፊያ ግቦች ዴዚሬ ዱዌ እና ኦስማን ዴምቤሌ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
ፒ ኤስ ጂ በግማሽ ፍጻሜው ከሪያል ማድሪድ እና ቦሩሺያ ዶርትመንድ አሸናፊ ጋር የሚጫወት ይሆናል፡፡
ምሽት 5 ሰዓት ላይ ሪያል ማድሪድ ከቦሩሺያ ዶርትመንድ ለግማሽ ፍጻሜው ለማለፍ ይፋለማሉ፡፡
የእንግሊዙ ቼልሲና የብራዚሉ ፍሉሚኒንሴ ቀደም ሲል ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡
በአቤል ንዋይ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡