ፕሬዚዳንት ትራምፕ በፍጻሜው ጨዋታ ስታዲየም ይገኛሉ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የክለቦች ዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታን ለመታደም ስታዲየም ይገኛሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሜት ላይፍ ስታዲየም በመገኘት የፍጻሜውን ጨዋታ እንደሚመለከቱ ዴይሊ ሜል ስፖርት ዘግቧል፡፡
በአዲስ አቀራረብ 32 ቡድኖችን አሳትፎ ውድድሩን የጀመረው የ2025 የክለቦች ዓለም ዋንጫ አሁን ላይ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡
በአሜሪካ አስተናጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው ውድድሩ ከአየር ንብረት እና ከተመልካች እጥረት ጋር በተያያዘ ትችት ሲቀርብበት ቆይቷል፡፡
አስቀድሞ ፍጻሜውን የተቀላቀለው ቼልሲ ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ከሚጫወቱት ሪያል ማድሪድ እና ፒኤስጂ አሸናፊ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል፡፡
የክለቦች ዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ በሜት ላይፍ ስታዲየም የፊታችን እሑድ የሚካሄድ ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!