Fana: At a Speed of Life!

አቶ ጀማል አሕመድ በደቡብ ካሎሪና ተወካዮች ም/ቤት እውቅና ተሰጣቸው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አሕመድ በደቡብ ካሎሪና ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የእውቅና ሰርተፊኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡

አቶ ጀማል እውቅና የተሰጣቸው ሚድሮክ በእርሳቸው አመራር ሰጪነት ኢትዮጵያ በተለያዩ ምርቶች በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንድትሆን ላበረከቱት አስተዋጽኦ ነው፡፡

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በግብርና እና አግሮ ፕሮሰሲንግ ዘርፍ በመሰማራት ኢትዮጵያ በዘርፉ አመርቂ ውጤት እንድታስመዘገብ ጉልህ ሚና መጫወቱ ተመላክቷል፡፡

የቡና፣ ሻይ ቅጠልና ሌሎች ምርቶችን ለውጪ ገበያ በማቅረብ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ እንድትሆን ማስቻሉም ተጠቅሷል፡፡

ከግብርና ባሻገር በኢንዱስትሪና ሌሎች ዘርፎች የተሰማራው ሚዲሮክ ኢትዮጵያ ለጀመረችው አካታችና ዘላቂ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ መገለጹንም ድርጅቱ ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.