Fana: At a Speed of Life!

የመጅሊስ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሐምሌ 13 ይጠናቀቃል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የመጅሊስ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሐምሌ 13 ቀን 2017 ዓ.ም ይጠናቀቃል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ሰብሳቢ አብዱላዚዝ ኢብራሂም (ዶ/ር) እንዳሉት፤ “ምርጫ ለጽኑ ተቋም” በሚል መሪ ሀሳብ ለሚካሄደው የመጅሊስ ምርጫ ከሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ ይገኛል።

የመራጮች ምዝገባው በመጪው እሁድ ሐምሌ 13 ቀን 2017 የሚጠናቀቅ በመሆኑ ለመራጭነት ያልተመዘገበው ሙስሊሙ ማኅበረሰብ የምርጫ ካርድ እንዲወስድ ጥሪ አስተላልፈዋል።

የመጅሊስ አመራሮች የቅድመ የምርጫ ሂደቱ 98 በመቶ መከናወኑን ገልጸው፤ ምርጫው ከነሐሴ 9 እስከ 11 ቀን 2017 በመላው ሀገሪቱ ምርጫው ይካሄዳል ብለዋል።

ህዝበ ሙስሊሙ ይመራኛል የሚለውን አመራር ለመምረጥ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የመጅሊስ አመራሮች ምርጫ ከተካሄደ በኋላም የሚመረጠው የመጅሊስ አመራር ለቀጣይ አምስት ዓመታት ህዝበ ሙስሊሙን የሚመራ ይሆናል።

በፈቲያ አብደላ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.