በሩሲያ የመንገደኞች አውሮፕላን ተከስክሶ የ49 ሰዎች ሕይወት አለፈ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሩሲያ ምስራቃዊ ክፍል አሙር ግዛት በመንገደኞች አውሮፕላን ላይ በደረሰ የመከስከስ አደጋ የ49 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
የሩሲያ የአደጋ ጊዜ አገልግሎት አመራሮች እንዳሉት÷ በዛሬው ዕለት 49 መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ አውሮፕላን በሩሲያ ምስራቃዊ ክፍል አሙር ግዛት አካባቢ ከራዳር እይታ ውጪ ሆኖ ተከስክሷል፡፡
በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ አምስት ሕጻናትን ጨምሮ 43 መንገደኞችና 6 የበረራ ሠራተኞችን በአጠቃላይ የ49 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተናግረዋል፡፡
አንቶኖቭ ኤኤን-24 የተሰኘው የመንገደኞች አውሮፕላን ከአሙር ግዛት ብላጎቨሽቼንስክ ወደ ቲይንዳ አውሮፕላን ማረፊያ እያመራ እንደነበር ሞስኮው ታይምስ ዘግቧል፡፡