ኮርፖሬሽኑ ከ4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አገኘ
አዲስ አበባ፣ሐምሌ 22፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ4 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ አግኝቻለሁ አለ፡፡
ኮርፖሬሽኑ የ2017/18 በጀት ዓመት ዕቅድና አፈፃፀም ግምገማ በጅማ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሰሃ ይታገሱ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በ2017 በጀት ዓመት የተኪ ምርቶች በ11 ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች እና በሁለት የኢንዱስትሪ ፓርኮች ተመርተዋል፡፡
በተጨማሪም 6 ቢሊየን ብር የሚገመት የገበያ ትስስር ለመፍጠር ታቅዶ 14 ቢሊየን ብር ግምታዊ የገበያ ትስስር መፈጠሩን ተናግረዋል።
ወደ ውጪ ከተላኩ ምርቶች 124 ሚሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱንና ለ48 ሺህ 900 ዜጎች የስራ ዕድል መፈጠሩን ጠቁመዋል፡፡
በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የዕቅዱን 99 በመቶ ማሳካት መቻሉን የገለጹት ፍሰሃ (ዶ/ር)÷ በቀጣይ የኢንዲስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት ሰፊ የስራ ዕድል ለመፍጠር በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
በበሪሳ ኃ/ማርያም
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!