Fana: At a Speed of Life!

ኮርፖሬሽኑ በማያ ከተማ አስተዳደር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄደ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በኦሮሚያ ክልል ማያ ከተማ አስተዳደር የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሂዷል።

የኮርፖሬሽኑ ሠራተኞች ከከተማዋ ነዋሪዎች ጋር በመሆን በባቴ ቀበሌ ቱሉቦ ተራራ ላይ የተለያዩ ሀገር በቀል ችግኞችን ተክለዋል፡፡

የፈዴራል ቤቶችና ኮርፖሬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ ረሻድ ከማል በዚሁ ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት 6 ዓመታት የተተከሉ ችግኞች ተዛብቶ የነበረውን የተፈጥሮ ሀብትና የአየር ንብረት እንዲስተካከል አድርጎታል፡፡

የሚተከሉ ችግኞች የአፈር መሸርሸር እንዳይከሰት እያደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ኮርፖሬሽኑ ቤቶችን በዘመናዊ መንገድ ገንብቶ ለተጠቃሚዎች ከማቅረብ በተጨማሪ በችግኝ ተከላና በሌሎች ተግባራት ላይ በመሳተፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

በምንያህል መለሰ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.