Fana: At a Speed of Life!

በክልሉ በተደረገ የግብርና ምርታማነትን የማሳደግ ንቅናቄ አዳዲስ ምርቶችን ማምረት ተጀምሯል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተደረገ የግብርና ምርታማነትን የማሳደግ ንቅናቄ በርካታ ወረዳዎች አዳዲስ ምርቶችን ማምረት ጀምረዋል።

በክልሉ በተለያዩ ዞኖች የሚገኙ በርካታ ወረዳዎች ከዚህ በፊት የማያመርቷቸውን የጥራጥሬ፣ የሰብል፣ የፍራፍሬ እና የእንስሳት ምርቶች እያመረቱ ነው፡፡

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ልማት ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር እንዳሉት፤ ግብርናን በማዘመን ምርታማነትን ለማሳደግ በስፋት እየተሰራ ነው።

ለክልሉ ሥነ ምህዳር ተስማሚ የሆኑ አዳዲስ ምርቶችን የማስተዋወቅ ሥራ እየተሰራ እንደሆነ ጠቅሰው፤ በዚህም በርካታ ወረዳዎች ከዚህ ቀደም የማያለሟቸውን ምርቶች ወደ ማልማት ገብተዋል ነው ያሉት።

በዚህም ቀደም ሲል በሶስት ወረዳዎች ብቻ ይመረት የነበረው የሙዝ ተክል በአሁኑ ወቅት ወደ 16 ወረዳዎች እንዲስፋፋ መደረጉን ገልጸዋል።

24 ወረዳዎች ፓፓያ 44 ወረዳዎች ደግሞ አቮካዶ ማምረት መጀመራቸውን ጠቁመዋል።

የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ በኩታ ገጠም እርሻ ምርታማነትን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

በታሪክ አዱኛ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.