Fana: At a Speed of Life!

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 የስታርታፕ ቢዝነሶች እንዲስፋፉ እያደረገ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ኢኒሼቲቭ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ነጥረው እንዲወጡ እና ስታርታፕ ቢዝነሶች እንዲስፋፉ እያደረገ ነው አለ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፡፡

ኢኒሼቲቩ ሀገራዊ የቴክኖሎጂ ሥነምህዳር እንዲመሰረት ማስቻሉም ተገልጿል።

የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር አማካሪ አብዮት ባዩ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ በኢኖቬሽን እና አርቲፊሻል አንተለጀንስ በርካታ ወጣቶችን የግዙፍ ኩባንያዎች ባለቤት ለማድረግ እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል፡፡

መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት ሰፊ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማቶች መሰራታቸውን ጠቅሰው÷ ዘንድሮ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመረቁ ተማሪዎች የራሳቸውን ቢዝነስ እንዲመሰርቱ እድል እየተመቻቸ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

ሁለተኛው ዙር ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ኢኒሼቲቭ ይቀጥላል ያሉት አብዮት (ዶ/ር)÷ ዲጂታላይዜሽን ለስራ እድል ፈጠራ እና የፈጠራ አቅምን ለማጎልበት አቅም ይፈጥራል ብለዋል።

በጸጋዬ ንጉስ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.