የኢትዮጵያን ፀጋ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ሚና ያለው ኪን-ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ኪን-ኢትዮጵያ የጥበብና ባህል ጉዞ የኢትዮጵያን ፀጋ ለዓለም ለማስተዋወቅ ጉልህ ሚና አለው አሉ።
በሩሲያ የሚደረገውን ሁለተኛው የኪን ኢትዮጵያ ጉዞ በተመለከተ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እና የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከሻኩራ ፕሮዳክሽን ጋር በመሆን መግለጫ ሰጥተዋል።
አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ በመግለጫው እንዳሉት፤ ኪን-ኢትዮጵያ የጥበብና ባህል ጉዞ ኢትዮጵያን በልኳ ለዓለም የማስተዋወቅ ዓላማ አለው።
እንዲህ ዓይነት የጥበብና ባህል ጉዞ በህዝብ ለህዝብ ግንኙነትና ፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራዎች ውስጥ አስፈላጊ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው ብለዋል።
ከዚህ በፊት ለሶስት ቀናት በቻይና ቆይታ የነበረው ኪን- ኢትዮጵያ በሀገራቱ መካከል ያለውን የመንግስት ለመንግስት ግንኙነት በህዝብ ለህዝብ ትስስር ለማጠናከር አስተዋጽኦ ማበርከቱን ተናግረዋል።
ጉዞው በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ሽፋን ያገኘ ሁነት እንደነበር አስታውሰዋል።
ጉዞው የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጭ ለማስተዋወቅ እድል የፈጠረ እና ቀጣይነት ያለው የህዝብ ለህዝብ ትስስር፣ ንግድና ኢንቨስትመንት ልውውጥ የሚያናክር እንደሆነ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን መልክ ለዓለም በማስተዋወቅ ረገድም ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል።
የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) በበኩላቸው፤ 2ኛው የኪን ኢትዮጵያ ጉዞ ከጳጉሜ 4 ቀን 2017 እስከ መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም በሩሲያ ይካሄዳል ብለዋል።
በሞስኮ ሴንት ፒተርስበርግና በሚካሄደው የጥበብ ትዕይንት የተለያዩ ሁነቶች እንደሚካሄዱ ገልጸው፤ የኢትዮጵያና ሩሲያን የባህል ትስስር የበለጠ ለማጠናከር እንደሚያግዝ ጠቁመዋል።
በሩሲያ በሚካሄደውና ከ60 በላይ ሀገራት የባህልና ጥበብ ተወካዮች በሚሳተፉበት የዩናይትድ ካልቸራል ፎረም ላይ በጉዞው የሚሳተፈው የኪን ኢትዮጵያ ቡድን የተለያዩ ትዕይንቶችን እንደሚያቀርብም ነው የተናገሩት።
በዮናስ ጌትነት
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!