Fana: At a Speed of Life!

የኅብር ቀን በሲዳማ ክልል በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኅብር ቀን “ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በሚል መሪ ቃል በሲዳማ ክልል በተለያዩ መርሐ ግብሮች እየተከበረ ይገኛል፡፡

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ በየነ ባራሳ በመርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ኢትዮጵያ በብዝሀ ማንነቶች የጠነከረች የሁላችንም ቤት ናት ብለዋል፡፡

የኅብር ቀን በአንድነትና በራስ አቅም ገንብተን የጨረስነውን ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለማስመረቅ በተጋጀንበት ወቅት የሚከበር መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገው አመልክተዋል፡፡

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በመልዕክታቸው፥ ውበትና ጸጋችን የሆነው ኅብራዊነት ጎልብቶ ታሪክ እንድንሰራ አስችሎናል ብለዋል።

በክልሉ በሁሉም መስኮች ድል ማስመዝገብ እንደተቻለ ገልጸው፥ ብሄር ብሄረሰቦች ያለምንም ችግር እሴቶቻቸውን እያጎለበቱ በክብርና በአንድነት የሚኖሩበት የብዝሃነት መገለጫ ክልል መፍጠር መቻሉን ጠቁመዋል።

በኅብር ቀን አከባበር መርሐ ግብር ላይ የክልሉ ሴክተር ቢሮዎች ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጇቸው ልዩ ልዩ ሁነቶች ተካሂደዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.