የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ አዲስ አበባ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ ቆይታቸው በአፍሪካ-ካረቢያን ማህበረሰብ ጉባኤ እና በ2ኛው የአፍሪካ አየር ንብረት ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ቦሌ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል።