Fana: At a Speed of Life!

የኅብር ቀን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ ዝግጅቶች ተከበረ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኅብር ቀን ‎”ብዝኃነት የኢትዮጵያ ጌጥ” በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ ዝግጅቶች ተከብሯል።

በበዓሉ ላይ ኅብር፣ አንድነት፣ የጋራ እሴቶችን የሚያንፀባርቁ የተለያዩ ኩነቶች የቀረቡ ሲሆን፥ ዕለቱን በማስመልከት የማዕድ ማጋራትና የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ብርሃኑ ጸጋዬ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ኢትዮጵያውያን ያጋጠሙንን ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች በህብር የመከትን ጠንካራ የአብሮነት እሴት ያለን የጥቁር ህዝቦች የኩራት ምንጭ የሆነ አኩሪ ገድልን በጋራ የፃፍን ህዝቦች ነን።

የተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮችን እንዲሁም በውጭ የሚገኙ ሚሲዮኖችን በማስተባበር ተቋሙ ድጋፍና እንክብካቤ ለሚያደርግላቸው 33 ታዳጊ ህፃናት የገንዘብ፣ የምግብ ግብዓቶች፣ የአልባሳትና የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉንም አመልክተዋል።

በተጨማሪም በተቋሙ ዝቅተኛ ደሞዝ ተከፋይ ለሆኑ ሰራተኞች አዲሱን ዓመት በማስመልከት የማዕድ ማጋራት በማድረግ ዕለቱን አክብረናል ብለዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.