Fana: At a Speed of Life!

የእመርታ ቀን የልማት እመርታዎችን እየደመርን ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገር የምንጀምርበት ነው – አቶ ኦርዲን በድሪ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የእመርታ ቀን የልማት ጉዞ እመርታዎችን እየደመርን ወደ አዲስ ምዕራፍ ማሸጋገር የምንጀምርበት ነው አሉ የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ፡፡

የእመርታ ቀን “እመርታ ለዘላቂ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት እየተከበረ ይገኛል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ ዕለቱን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት፥ ይህ ቀን በሁሉም የብልጽግና ዘርፎች ክልላችንና ሀገራችንን ወደላቀ ዘላቂ እመርታ ለማድረስ የገባነውን ቃል ኪዳን የምናድስበት ነው ብለዋል።

የእመርታ ቀን በሀረሪ ክልልም ሆነ በሀገራችን አጠቃላይ የልማት ጉዞ እመርታዎችን በመደመር ወደ አዲስ ቀጣይ ምዕራፍ ማሸጋገር የሚጀመርበት ዕለት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በመተጋገዝና አንድነታችንን በማጠናከር “እመርታ ለዘላቂ ከፍታ” የሚለውን መሪ ቃል እውን ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ሁሉም በተሰማራበት የሙያና የኃላፊነት መስክ ዘላቂነት ያለው ፈጣን እመርታ ለማረጋገጥና ለቀጣይ ትውልድ የበለፀገ ክልልና ሀገር ለማስረከብ በላቀ ትጋት፣ በጋለ መነሳሳትና በማያቋርጥ ጥረት እንዲንቀሳቀስ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.