የባሕር ዳርን የኮሪደር ልማት ከጣና ውበት ጋር ለማሰናሰል…
አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 3፣ 2017 (ኤፍ ኤምሲ) የባሕር ዳርን የኮሪደር ልማት ከጣና ውበት ጋር በማገናኘት ከተማዋን ለኑሮ ምቹና ለቱሪዝም ተመራጭ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡፡
ጳጉሜን 3 የእመርታ ቀን በባሕር ዳር የመንግስት የሥራ ሃላፊዎችና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ተከብሯል፡፡
የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ም/ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በሁሉም መስኮች ምርታማነትን የማሳደግና ዘመናዊ ከተማ የመገንባት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የባሕር ዳርን የኮሪደር ልማት ከጣና ውበት ጋር በማገናኘት ከተማዋን ለኑሮ ምቹና ለቱሪዝም ተመራጭ ማድረግ እየተቻለ መሆኑን ጠቁመው÷ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
በኮሪደር ልማቱ የጣናን ውበት በመግለጥ፣ የዓባይ ድልድይና የ22 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገዶችን በጥራት በማከናወን የተሰናሰሉ የልማት ሥራዎችን ማሳካት መቻሉንም ተናግረዋል።