Fana: At a Speed of Life!

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከሲአይኤፍኤፍ የቦርድ ሊቀመንበር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከችልድረን ኢንቨስትመንት ፈንድ ፋውንዴሽን (ሲአይኤፍኤፍ) መስራች እና የቦርድ ሊቀመንበር ሰር ክሪስቶፈር ሆን ጋር ተወያይተዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ሰር ክሪስቶፈር ሆን ኢትዮጵያ በምግብ እና ሥርዓተ ምግብ ስትራቴጂ፣ በሰቆጣ ቃል ኪዳን፣ በግሪን ኢነርጂ፣ በእናቶች፣ በሴቶች እና በህጻናት ጤና ላይ እየሰራች ያለዉ ስራ የሚበረታታ መሆኑን ነግረውኛል ብለዋል።

በእነዚህ ጉዳዮች ላይ ሲአይኤፍኤፍ ድጋፉን እንደሚያጠናክር ሊቀመንበሩ ቃል መግባታቸውን ጠቅሰው፤ ድርጅቱ ሕዝብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በተለይ በንጹህ ውሃ አቅርቦትና በሴቶች የስራ እድል ፈጠራ ላይ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል ነው ያሉት፡፡

በተጨማሪም ሊቀ መንበሩ የኢትዮጵያ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም በዕጅጉ እንዳስደነቃቸው ተናግረዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.