Fana: At a Speed of Life!

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የብልጽግና ጅማሮ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ተከትሎ በባሕር ዳር ከተማ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

በሰልፉ ላይ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ቢዚህ ወቅት÷ ኢትዮጵያ የነጻነት ባለቤት መሆኗን የማይፈልጉ ጠላቶች ሲገፏት እና ሲወጓት መኖራቸውን አንስተው÷ ኢትዮጵያውያን ግን ማሸነፍ ልምዳቸው ነውና ድል ሲያደርጉ ኖረዋል ብለዋል።

ኢትዮጵያን ከደህንነት እና ከግጭት ለማውጣት ሥራ መጀመሩን ገልጸው÷ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የብልጽግና ጅማሮ መሆኑን አንስተዋል።

ሕዳሴ የአሸናፊነት ማሳያ፣ የብልጽግና ጉዞ ማብሰሪያ፣ የአንድነት ማሳያ እንዲሁም በአንድነት ማሳካት የማንችለው እንደሌለ ያሳየ ዳግማዊ ዓድዋ ነው ሲሉም ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ያሰበችውን እያሳካች ትቀጥላለች፤ የሚያቆማት የለም ያሉት ከንቲባው÷ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች ለሀገር የሚጠበቅባቸውን ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.