Fana: At a Speed of Life!

ሕዝባችን ሰላም ወዳድና ልማት ፈላጊ መሆኑን በተግባር አሳይቷል – አቶ አረጋ ከበደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሕዝባችን ትናንትም ሆነ ዛሬ ሰላም ወዳድ እና ልማት ፈላጊ መሆኑን በተግባር አሳይቷል አሉ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን አስመልክቶ በአማራ ክልል ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ መካሄዱን አንስተዋል፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱ ለኢትዮጵያ ብሎም ለክልሉ ሕዝብ ታላቅ ትርጉም እንዳለው አስገንዝበዋል፡፡

የሕዳሴ ግድበን ተጨማሪ አቅም በመጠቀም የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሚሰራም አመልክተዋል፡፡

ሕዳሴ ግድብ በርካታ ዲፕሎማሲያዊ ተግዳሮቶችን ተሻግረን በራሳችን ሃብት፣ ጉልበትና እውቀት የዘመናት የፀና ፍላጎታችንና የዓመታት ልፋታችንን ወደ ውጤት ቀይረን ያረጋገጥንበት ነው ሲሉም ተናግረዋል።

አይሳካላቸውም በሚል ሲዘባበቱ የነበሩ የጠላቶቻችንን ትርክት ጥሰንና በጣጥሰን ሕዳሴያችን በጋራ አጠናቅቀን ለድል በቅተናል ያሉት አቶ አረጋ÷ በዚህም ለቀጠናው ሀገራትና ለመላ አፍሪካውያን ዳግም ተምሳሌት መሆን ችለናል ብለዋል።

ታላቁ የሕዳሴ ግድብ የዘመኑ ትውልድ የልማት አርበኝነት የተረጋገጠበት እና ለመጪው ትውልድ የሚተላለፍ ሁለተኛው የዓድዋ ድል መሆኑን አውስተዋል፡፡

የሕዳሴ ግድብ የሃይል አቅርቦት ፍላጎት በዘላቂነት ከመቅረፍ ባለፈ የዜጎችን የአኗኗር ዘይቤ እንደሚቀይር ጠቁመዋል።

ከግጭት አዙሪት ወጥተን፣ የጋራ ታሪካችን ጠብቀን እና ጸጋዎቻችን በአግባቡ ተጠቅመን ሌላ ድል ለማስመዝገብ በጋራ መቆም ይኖርብናል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ የተካሄዱ የድጋፍ ሰልፎች በሰላም እንዲጠናቀቁ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አመራሮች፣ የጸጥታ አካላት እና ለመላው ሕዝብ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.