Fana: At a Speed of Life!

ሕዝባዊ እና ሃይማኖታዊ በዓላት የኢትዮጵያ ብዝኃነት ማሳያ ናቸው – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመስቀል ደመራ በዓል ኢትዮጵያ በዓለማቀፍ ደረጃ በማይዳሰስ ቅርስነት ካስመዘገበቻቸው መካከል አንዱ ነው፡፡

በዓሉ በመላው ኢትዮጵያ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተወራረሰ እና ተጠብቆ የቀጠለ ክዋኔን የሚያሳይ የኢትዮጵያ ብዝኃነት እና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት ማሳያ ነው፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ ሳይንስ እና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበዉም ይህንን ነባር የአከባበር ትውፊቱን ይዞ እንዲቀጥል፣ ከኢትዮጵያ አልፎ የሰው ልጆች ኹሉ የጋራ ቅርስነቱ እንዲጠበቅ ለማስቻል ነው፡፡

ኢትዮጵያውያንም የመስቀል ደመራ በዓልን በየዓመቱ ጥንታዊነቱንና ማኅበራዊ እሴቱን ጠብቀዉ ያከብሩታል፡፡ መንግሥት ልዩ ትኩረት ከሰጣቸዉ የኢኮኖሚ ዘርፎች አንዱ ለኾነው የቱሪዝም ዕድገትም የራሱን ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

የዘንድሮዉን የመስቀል ደመራ በዓል የምናከብረዉ ደግሞ ኢትዮጵያውያን በጋራ ያሳካነውን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ድልን እያከበርን ባለንበት ወቅት ነው፡፡ ይህም በዓሉን የበለጠ ደማቅ ያደርገዋል፡፡

እንኳን ለመስቀል ደመራ በዓል አደረሳችሁ!
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.