የመስቀል በዓል በመላ ሀገሪቱ ተከበረ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመስቀል በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በመላ ሀገሪቱ ተከበረ።
በዓሉ በተለያዩ ሐይማኖታዊ እና ባህላዊ ሥነ ሥርዓቶች ነው በድምቀት የተከበረው።
በትናንትናው ዕለት የመስቀል ደመራ በመላ ሀገሪቱ በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ በደማቅ ሥነ ሥርዓት መከበሩ ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርቲያን ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በትናንትናው ዕለት በመስቀል ደመራ በዓል ላይ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፥ በዓሉን በይቅርታ፣ በፍቅር፣ በመተሳሰብ እና በእርቅ ማክበር እንደሚገባ አሳስበዋል።