Fana: At a Speed of Life!

የሥነ ሕዝብ ትሩፋትን በሥነ ተዋልዶ ጤና ለማሳደግ የሚረዳው ፕሮጀክት…

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የጤና ሚኒስቴር ከአፍሪካ ህብረት ልማት ኤጀንሲ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎትን ማሻሻል የሚያስችል የአምስት ዓመት ፕሮጀክት አስጀምሯል፡፡

በኢትዮጵያና አፍሪካ ሀገራት በፍጥነት እያደገ የመጣውን የወጣቶች ቁጥር እና አሳሳቢ የጤና አገልግሎት ፍላጎቶች ለሟሟላት ፕሮግራሙ ወሳኝ ጊዜ ላይ መጀመሩን ተመላክቷል፡፡

ጥራት ያለው የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎትን ተደራሽነት በማረጋገጥ ለተሻሻሉ የጤና ውጤቶች እና ለላቀ የኢኮኖሚ ምርታማነት አስተዋፅኦ እንደሚያበረከትም ተጠቅሷል።

ፕሮጀክቱ ከኢትዮጵያ የጤና ፖሊሲ ጋር የተጣጣመ ሲሆን ÷ የወጣቶችን ሥነ ተዋልዶ ጤና በሃገር አቀፍ ደረጃ ያሻሽላል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.