Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ የዓለም የገንዘብ ሥርዓት ፍትሃዊና አካታች እንዲሆን ጥሪ አቀረበች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የዓለም የገንዘብ ሥርዓት በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን ዘላቂ ልማት ታሳቢ ያደረገ እና ፍትሃዊ እንዲሆን ጥሪ አቅርባለች፡፡

የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ ከዓለም ባንክ እና ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዓመታዊ ስብሰባ ጎን ለጎን እየተካሄደ በሚገኘው 114ኛው የቡድን 24 ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል፡፡

በመድረኩ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስትሊና ጆርጂየቫ እና የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አና ቤርዴን ጨምሮ የአባል ሀገራቱ የፋይናንስ ሚኒስትሮች ተገኝተዋል፡፡

ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት ባደረጉት ንግግር ፥ ለታዳጊ ሀገራት ፍትሃዊ የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የዓለም የገንዘብ ሥርዓት ሊኖር እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

የቡድን 24 አባል ሀገራት በቡድን 20 የጋራ ማዕቀፍ መሰረት የዕዳ ሽግሽግ ሒደት ተግባራዊ እንዲደረግ ያቀረቡት ጥሪ ወቅቱን የጠበቀ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ ፥ በዚህ ረገድ ያከናወናቸውን ተግባራት አድንቀዋል፡፡

የዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ማኔጂንግ ዳይሬክተሮች በዚሁ ወቅት ተቋሞቻቸው ከቡድን 24 ስብስብ ጋር የሚያከናውኗቸውን ተግባራት አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል፡፡

በአባል ሀገራቱ እየተከናወኑ የሚገኙ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን አድንቀው ፥ ዘላቂና አካታች ልማት እንዲሁም የተረጋጋ የፋይናንስ ሥርዓትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ማሻሻያዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast  YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.