ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የካቶሊክ የርዳታ ድርጅት የልማት ስራዎችን አደነቁ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የካቶሊክ የርዳታ ድርጅት (ሲ አር ኤስ) በኢትዮጵያ እያከናወናቸው ያሉትን የልማት ስራዎች አድንቀዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ታዬ ከኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነኢየሱስ ሱራፌል እና ከድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሻን ካላሃን ጋር ተወያይተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የካቶሊክ የርዳታ ድርጅት በኢትዮጵያ በተለይም አርሶ እና አርብቶ አደሮችን በመደገፍ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ድርጅቱ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀው፥ በቀጣይም ለሚያከናውናቸው ተግባራት መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል፡፡
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!