Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለጀመሩት ፕሮጀክት ድጋፍ ላደረጉ ለጋሾች የእራት ግብዣ አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጀመሩት የአዳራሽ እና አካባቢን የማስዋብ ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ ለጋሾች የእራት ግብዣ አድርገዋል።

አዲሱን የኋይት ሀውስ ታላቅ አዳራሽ እና አካባቢን የማስዋብ የ200 ሚሊየን ዶላር ፕሮጀክት የሚደግፉ ለጋሾችን እና ባለሃብቶችን በነጩ ቤተ መንግስት እራት ጋብዘዋል።

ባለፈው መስከረም ወር ግንባታ የጀመረው እና 90 ሺህ ስኩዌር ጫማ የሚሸፍነው አዳራሽ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶችን ያስተናግዳል።

እንደ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ገለጻ፤ ፕሮጀክቱ አሜሪካን በዓለም መድረክ በተሻለ ሁኔታ እንዲወክል የሚያስችል ነው።

አሁን ላይ ያለው መሠረተ ልማት መሪዎችን ለመቀበል እና ለማነጋገር ብሎም የተለያዩ ሁነቶችን ለማስተናገድ ምቹ አለመሆኑንም አንስተዋል።

የታላቁ አዳራሽ ፕሮጀክት ከኋይት ሀውስ ንድፍ ጋር የሚስማማ ተደርጎ እንደሚገነባ ገልጸው፤ ለፕሮጀክቱ ድጋፍ እያደረጉ ለሚገኙ ባለሃብቶችን እና ኩባንያዎች አመስግነዋል።

በእራት ግብዣው ላይ የማይክሮሶፍት፣ የሜታ፣ የጉግል፣ የአማዞን እና የቲ-ሞባይል ተወካዮችን ጨምሮ በርካታ የክሪፕቶ ስራ ፈጣሪዎች እና ባለሃብቶች ተገኝተዋል ሲል ሲኤንኤን ዘግቧል።

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ዛሬ ላይ የጀመሩት ‘የሌጋሲ ዲነር’ ስራ ከዓመታት በፊት በአዲስ አበባ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጭነት የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት በሚል መጀመሩ ይታወቃል።

ዜጎች እና ባለሀብቶች የነቃ ተስትፎ ባደረጉበት የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ከአዲስ አበባ ውጪ በሶስት ቦታዎች ማለትም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮይሻ፣ በአማራ ክልል ጎርጎራ፣ በኦሮሚያ ክልል ደግሞ ወንጪን ማልማት መቻሉ ይታወቃል።

በዮናስ ጌትነት

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.