የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ መካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በዛሬው ዕለት መካሄድ ጀምሯል።
ጉባዔውን አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በፀሎት አስጀምረዋል።
በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት እንዳሉት፤ በተለያዩ መንገዶች እየተከናወኑ የሚገኙ ቤተክርስቲያንን የመዳፈር ተግባራት ለመፍታት በሕግ አግባብ መንቀሳቀስ ይገባል።
የነገ ትውልድ ልማታዊ ተስፋ እውን የሚሆነው ሰላምና አንድነት ሲኖር በመሆኑ ሁሉም ለሀገር ሰላምና አንድነት ሊሰራ እንደሚገባ ጠቁመው፤ ለዚህም ጉባዔው የበኩሉን ጥረት እንዲያደርግ አሳስበዋል።
በምልዓተ ጉባዔው ላይ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት የመጡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የተገኙ ሲሆን በቤተክርስቲያኗ እና በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ምክክር ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
በዙፋን ካሳሁን
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!