Fana: At a Speed of Life!

ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች መሸርሸር በሚሊየን የሚቆጠር ህይወትን አደጋ ላይ ጥሏል – አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች መሸርሸር በሚሊየን የሚቆጠር ህይወትን አደጋ ላይ ጥሏል አሉ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፡፡

151ኛው የዓለም የፓርላማ ሕብረት (አይፒዩ) ጉባኤ በችግር ጊዜ የሰብአዊነት ድንጋጌዎችን ማክበር እና የሰብአዊ ርምጃዎችን መደገፍ በሚል መሪ ሐሳብ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር የጋራ ሰብአዊነታችን መሠረት የሆነው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌ መሸርሸር በሚሊየን የሚቆጠር ሕይወት አደጋ ላይ ጥሏል ብለዋል፡፡

ድንጋጌዎቹ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ተጽዕኖ ውስጥ መግባታቸውንና በዓለም ዙሪያ ሲቪሎች፣ የሰብአዊ እርዳታ ሠራተኞች እና የሕክምና ባለሙያዎች በግጭት እና በአመጽ እየተጎዱ መሆናቸውን አንስተዋል።

የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን ማክበር ሕጋዊ ብቻ ሳይሆን ሥነ ምግባራዊ ግዴታ ነው ያሉት አፈ ጉባኤው÷ ፓርላማዎች ከመቼውም ጊዜ በላይ በአሁኑ ወቅት እነዚህን መርሆች የመጠበቅ፣ የባለ ብዙ ወገን ግንኙነት የማጠናከር፣ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች እንዲጠበቁና በበቂ ሁኔታ እንዲደገፉ ለማድረግ የሞራል እና የፖለቲካ ግዴታ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከድንጋጌዎቹን በፅኑ እንደምታከብር እና አራቱን የጄኔቫ ስምምነቶችንና ተጨማሪ ፕሮቶኮሎችን የሕገመንግሥቱ እና የሌሎች ሕጎች አካል ማድረጓን መግለፃቸውን የምክር ቤቱ ጽ/ቤት የኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ተረፈ በዳዳ ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.