Fana: At a Speed of Life!

ሉሲዎቹ በታንዛኒያ አቻቸው ተሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሴቶች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በታንዛኒያ አቻቸው 2 ለ 0 ተሸንፏል፡፡
ሉሲዎቹ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ የመጨረሻውን የማጣሪያ ጨዋታ 11 ሰዓት ላይ በታንዛኒያ አዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም ነው ከታንዛኒያ አቻቸው ጋር የተጫወቱት።
በጨዋታው የተሸነፉት ሉሲዎቹ÷ የመልስ ጨዋታውን ከሰባት ቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ያደርጋሉ፡፡
ኢትዮጵያ በሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ የተሳተፈችው በ2012ቱ የኢኳቶሪያል ጊኒ እንደነበር ይታወሳል፡፡
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.