Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል ከ16 ሚሊየን ኩንታል በላይ የቡና ምርት ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል በ2018 በጀት ዓመት የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተከናወኑ ሥራዎች ከ16 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ይገኛል ተብሎ ይጠበቃል አለ የክልሉ ግብርና ቢሮ፡፡

የቢሮው ም/ኃላፊ መሃመድሳኒ አሚን ለፋና ዲጂታል እንደገለጹት ፥ ባለፉት ዓመታት የቡና ምርትና ምርታማነትን እንዲሁም ጥራትን በማሳደግ ረገድ አበረታች ውጤት ተገኝቷል፡፡

አዳዲስ የቡና ኢኒሼቲቮችን በማስተዋወቅ፣ ምርምሮችን በማስፋት፣ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀምና ዘመናዊ አሰራሮችን በመተግበር በርካታ ሥራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡፡

በዚህም በክልሉ የቡና ምርት በእጥፍ የጨመረ ሲሆን ፥ በ2011 ዓ.ም በሄክታር ይገኝ ከነበረው 6 ኩንታል ምርት አሁን ላይ ወደ 9 ኩንታል ከፍ ማድረግ መቻሉን አመልክተዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ከ16 ሚሊየን ኩንታል በላይ ቡና ይመረታል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቅሰው ፥ በምርት አሰባሰብ ሒደት የአርሶ አደሩን ግንዛቤ በማሳደግ ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

የዘርፉን ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ ባሻገር ለጥራት ትኩረት በመስጠት በተሰሩ ሥራዎች በክልሉ ተመርቶ ለውጭ ገበያ የሚቀርበው ቡና መጠን በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን ተናግረዋል፡፡

ለአብነትም በ2017 በጀት ዓመት በክልሉ ተመርቶ ለማዕከላዊ ገበያ ከቀረበው ከ500 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ውስጥ 400 ሺህ ቶን ያህሉ ወደ ውጭ ተልኳል ነው ያሉት፡፡

በኃይለማርያም ተገኝ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.