Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ጋር መከሩ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአዲሱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ከአዲሱ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ሲዲ ኡልድ ታህ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተናል ብለዋል።

ምክክሩም ባንኩ በመላው አፍሪካ አካታች እድገት እንዲኖር የሚያደርገውን ወሳኝ ሚና ያጠናከረ እንደነበር አመልክተዋል፡፡

ውይይቱ በጆሃንስበርግ እየተካሄደ ከሚገኘው የቡድን 20 የመሪዎች ጉባዔ ጎን ለጎን ነው የተደረገው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.