Fana: At a Speed of Life!

የሸበሌ ሪዞርት ፕሮጀክት የማጠናቀቂያ ሥራ…

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሶማሌ ክልል የሚገኘውን የሸበሌ ሪዞርት ግንባታ በጥራትና በፍጥነት ለማጠናቀቀ በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡

የገበታ ለትውልድ የቱሪዝም ሥራዎች አካል የሆነው የሸበሌ ሪዞርት ፕሮጀክት የመጨረሻ ግንባታ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።

በመድረኩ የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር)፣ የክልሉ ም/ርዕሰ መስተዳድር ኢብራሂም ዑስማን እና ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

በዚህ ወቅትም የሸበሌ ሪዞርት ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ ሥራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተመላክቷል፡፡

የሸበሌ ሪዞርት ፕሮጀክት ግንባታን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡

ፕሮጀክቱን ለማስመረቅ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር መደረጉን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

ከጅግጅጋ 29 ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ በፋፈን ዞን የሚገኘው ሸበሌ ሪዞርት በ385 ሄክታር መሬት ላይ ነው ያረፈው፡፡

ሪዞርቱ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለክልሉና ለአከባቢው ከፍተኛ የቱሪስት መዳረሻ እንደሚሆን ይጠበቃል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.