Fana: At a Speed of Life!

በፍትሕ ዘርፉ የፎረንሲክ ምርመራ ሒደትን ለማጠናከር በትኩረት ይሰራል – ወ/ሮ ሃና አርአያሥላሴ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፍትሕ ዘርፉ የፎረንሲክ ምርመራ ሒደትን ለማጠናከር በትኩረት ይሰራል አሉ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርአያሥላሴ፡፡

በኢትዮጵያ ሲተገበር የቆየው የአውሮፓ ህብረት የወንጀል ፍትሕ ቴክኒካል ድጋፍ ፕሮግራም ማጠቃለያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ የፍትሕ ሚኒስትር ሃና አርአያሥላሴ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዚዳንት ቴዎድሮስ ምህረት እና በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ተገኝተዋል፡፡

ወ/ሮ ሃና አርአያሥላሴ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ የፍትሕ ሥርዓቱን ተደራሽነት ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡

የፍትሕ ሥርዓት መጠናከር ሰላማዊ፣ ዴሞክራሲያዊና የበለጸገች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የተጀመረውን ጥረት ለማሳካት እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡

የፍትሕ ሥርዓቱን ተአማኒነት፣ ተደራሽነትና አስተማማኝነት ማረጋገጥ ለብሔራዊ መረጋጋት፣ ለኢኮኖሚ እድገትና ለማህበራዊ ትስስር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለውም አስገንዝበዋል፡፡

የቴክኒካል ድጋፍ ፕሮግራሙ የፍትሕ ዘርፍ ተቋማት ትስስርና አገልግሎት እንዲጠናከር እንዲሁም የፎረንረሲክ ወንጀል ምርመራ ሒደት እንዲሻሻል ጉልህ ሚና መጫወቱን አብራርተዋል፡፡

በፎረንሲክ የታገዘና ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የሕዝቡን ሰላምና ደህንነት በመጠበቅ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እንሚሰራ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

አቶ ቴዎድሮስ ምህረት በበኩላቸው ÷ በፕሮግራሙ በስልጠና፣ በተሞክሮ መጋራት፣ በአቅም ግንባታ እና ሌሎች ዘርፎች ላይ የተከናወኑ ሥራዎች አበረታች ውጤት ማስገኘታቸውን አመልክተዋል፡፡

የፍትሕ ሥርዓቱን ለማጠናከር የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ ነው ያሉት አቶ ቴዎድሮስ ÷ የአውሮፓ ህብረትና ጂአይዜድ በዘርፉ ላደረጉት ድጋፍ አመስግነዋል፡፡

አምባሳደር ሶፊ ፍሮም÷ የአውሮፓ ህብረት በፍትሕ እና ሌሎች ዘርፍች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.