አቶ ሽመልስ በክላስተር የታረሰ የእርሻ ማሳን ጎበኙ
በአዳባ ከተማ አስተዳደርም 16 መኖሪያ ቤቶች እና 2 ሄቴሎች ጥቃት ተፈፅሞባቸው የነበረ ሲሆን በህብረተሰቡ እና በመንግስት ተሳትፎ 12 መኖሪያ ቤቶች ጥገና እንደተደረገላቸው የከተማዋ ከንቲባ አቶ ሙስጠፋ ዑመር ተናግረዋል ።
በርዕሰ መስተዳድሩ የሚመራው ልዑክ በተመሳሳይ በባሌ ዞን በምትገኝ አጋፋ ወረዳ ጉዳት የደረሰባቸው የመንግስት ተቋማትን የጎበኘ ሲሆን አቶ ሽመልስ አብዲሳ ከህብረተሰቡ ጋር በነበራቸው ቆይታ የመልሶ ማቋቋም ስራው በአፋጣኝ እንደሚጀምር ገልፀዋል።
በነበራቸው ቆይታ አብዛኛው ውድመት የደረሰበት የመንግስት ተቋም ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ህዝቡ እራሱ መልሶ እንዲገነባው አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡
ህብረተሰቡም ጉዳት አድራሾቹን በአፋጣኝ አጋልጦ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በወረዳው 38 የመንግስት ተቋማት መውደማቸው ታውቋል፡፡
በትዝታ ደሳለኝ