Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያን የእስልምና ጉዞ ከመነሻ እስካሁን የሚያሳይ ሙዝዬም ያደራጀው ቢላሉል ሐበሺ…

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መካኒሳ አካባቢ የሚገኘውን ቢላሉል ሐበሺ በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ እንዳሉት ÷ ቢላሉል ሐበሺ የኢትዮጵያ ታሪክ አካል የሆነውን የኢትዮጵያን የእስልምና ጉዞ ከመነሻ እስካሁን የሚያሳይ ሙዚዬም አደራጅቷል።

በሀገራችን የእስልምና ታሪካችንን የሚዘክሩ ሙዚዬሞች በጣት የሚቆጠሩ በመሆናቸው ይህ ሙዚዬም ታላቅ ዋጋ ያለው መሆኑን አውስተዋል፡፡

በሙዚዬሙ ውስጥ ከመጀመሪያው ሒጅራ አንሥቶ እስካሁን ያለው ታሪካችን በሚገባ ይታያል ብለዋል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን፡፡

ኢትዮጵያ የብዙ ሶሐባዎች ማረፊያ፣ የታላላቅ ዓሊሞች መገኛ፣ የአስደናቂ እስላማዊ ቅርሶች መናኸሪያ መሆኗንም ነው ያስገነዘቡት፡፡

ተቋሙ ወጣቶችን በሙያ አሠልጥኖ ለሥራ በማብቃት፣ ችግረኞችን በመርዳት፣ ጥናትና ምርምርን በመደገፍ፣ ለወጣቶች ተስማሚ መዋያ በማዘጋጀት የሚያደርገው አስተዋጽኦ እጅግ ታላቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቢላሉ ሐበሺ ዕድሮች አሁን ከያዙት ዓላማ በላይ በማከናወን የማኅበረሰብን ሕይወት ሊቀይሩ እንደሚችሉ አርአያ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ስለሆነም ተቋሙን በማገዝ ታሪካችንን መጠበቅና ወጣቶቻችንን ማብቃት አለብን ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.