በኦሮሚያ ክልል የቱሪስት መዳረሻዎችን በዓይነትና በጥራት መጨመር ተችሏል
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ክልል ቱሪዝም ኮሚሽን ባለፉት ዓመታት በተሰራ ስራ የክልሉን የቱሪስት መዳረሻዎች በዓይነትና ጥራት መጨመር ተችሏል አለ።
በኦሮሚያ ክልል ቱሪዝም ኮሚሽን ቢሮ አዘጋጅነት በዛሬው ዕለት በጅማ ከተማ የኦሮሚያን እንጎብኝ አካል የሆነ ‘ኮፊ ቱር’ የሳይክል ግልቢያ ተካሂዷል።
የክልሉ ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ በወቅቱ እንዳሉት፤ ባለፉት ዓመታት የቱሪስት መዳረሻዎችን የማልማት ስራ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶታል።
በዚህም የቱሪስት መዳረሻዎች በዓይነት እና በጥራት መጨመር ተችሏል ነው ያሉት።
የክልሉ ነባር የቱሪስት መዳረሻዎችን ለቱሪስት ምቹ ለማድረግ ከተሰራው ስራ ባሻገር የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም መንደር እና ሎጅን ጨምሮ በርካታ አዳዲስ መዳረሻዎችን የማልማት ተግባራት መከናወኑን ጠቅሰዋል።
የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በክልሉ ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠው ትኩረት ውጤታማ እና የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።
መንግሥት ለዘርፉ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በአብዱረህማን መሀመድ
ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Facebook https://web.facebook.com/fanasport
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!