Fana: At a Speed of Life!

ብፁዕ ካርዲናል ብርሐነ ኢየሱስ ለገና በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስትያን ሊቀጳጳሳት ብፁዕ ካርዲናል ብርሐነ ኢየሱስ የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ብፁዕ ካርዲናል ብርሐነ ኢየሱስ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የልደት በዓል የምስራች የሁሉም መሰረት የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መወለዱ እና በኛም መካከል ማደሩ ነው ብለዋል።

የልደት በዓልን ስናከብር ስለሰው ልጆች ክብር የምንሰራበት፣ ሕዝቦች የሚከባበሩበት፣ የሚዋደዱበትና የሚተሳሰቡበት ሊሆን ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል።

በተለያዩ ምክንያቶች ከቤት ስለራቁት በመፀለይ፣ ለአቅመ ደካሞች፣ ለህሙማን፣ በየጎዳናው ላሉ ወገኖች ያለንን በመስጠትና በማካፈል በዓሉን ማክበር እንደሚገባም የአደራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በቅድስት ተስፋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.