Fana: At a Speed of Life!

ላሊበላ የኢትዮጵያውያንን የቆየ የምህንድስና ጥበብ የሚያሳይ ነው – ጎብኚዎች

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት ኪነ ሕንጻ የኢትዮጵያውያንን የቆየ የምህንድስና ጥበብ የሚያሳይ ነው አሉ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ጎብኚዎች።

የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ለማክበር የተለያዩ ሀገራት ዜጎች በላሊበላ በመገኘት የገና ክብረ በዓልን በመታደም ላይ ይገኛሉ።

ከስፔን እንደመጡ የተናገሩ አንድ ጎብኚ እንደሚሉት፤ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት በጥንት ጊዜ የተሰራ ሳይሆን በአሁኑ ጊዜ ቴክኖሎጂዎች የተገነቡ የሚመስሉ የጥበብ ውጤቶች ናቸው።

በላሊበላ ሦሥተኛ ቀናቸውን እያሳለፉ የሚገኙት ጎብኚዋ፤ በዛሬው ዕለት በርካታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች በውብ ዝማሬ ሲያመሠግኑ መመልከታቸው ልዩ ደስታን እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል።

የሀገራቸው ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ይህንን ክብረ በዓል እንዲጎበኙ ያዩትን ለማድረስ ዝግጁ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ከሩሲያ የመጡት ሌላኛው ጎብኚ፤ ከአንድ አለት ተፈልፍለው የተሠሩ አብያተ ክርስቲያናትን ለመጀመሪያ ጊዜ በመመልከታቸው መደነቃቸውን ገልጸዋል።

የአካባቢው ማኅበረሠብ ሰላማዊ እና እንግዳ አክባሪነቱ ትኩረታቸውን እንደሳበው አንስተዋል።

የፍልፍል አብያተ ክርስቲያናቱ ሥራ የኢትዮጵያውያን የቆየ የምህንድስና ጥበብ የሚያሳይ ነው ያሉት ደግሞ ከእስራኤል የመጡ ጎብኚ ናቸው።

በቀጣይ ቀናት ሌሎች አካባቢዎችን እንደሚጎበኙ በመግለጽ፤ የማኅበረሰቡ እንግዳ ተቀባይነት ማራኪ እንደሆነ መግለጻቸውን የአማራ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation

Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting

Facebook https://web.facebook.com/fanasport

Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate

Telegram t.me/fanatelevision

Website www.fanamc.com

TikTok www.tiktok.com/@fana_television

WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29

Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment

TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment

Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.